Skip to content
Newsroom

ባለሥልጣኑ በአረንጓዴ አሻራ እና በክረምት በጎ ተግባራት ድጋፍ ላይ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ተወያየ

ETA Education & Training Authority August 04, 2026 1 min read
ባለሥልጣኑ በአረንጓዴ አሻራ እና በክረምት በጎ ተግባራት ድጋፍ ላይ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ተወያየ
ባለሥልጣኑ በአረንጓዴ አሻራ እና በክረምት በጎ ተግባራት ድጋፍ ላይ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ተወያየ
ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ባለሥልጣኑ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በአረንጓዴ አሻራ እና በክረምት በጎ ተግባራት ድጋፍ ላይ ውይይት አካሄደ ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው ሊሰሩ የታቀዱት የአፀደ ህጻናት እና የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታበቤንሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን መሆኑ ገልጸው በዚህ በጎ ተግባር የሚሳተፉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የእውቅና ሰርተፍኬት ፤የሚሰጡት ድጋፍ ከታክስ ነጻ እንዲሆን የሚያደርግ የድጋፍ ደብዳቤ ፤ከተቋማቸው ተልእኮ አንጻር የማህበረሰብ አገልግሎት እና የጥናትና ምርምር ሥራዎች ጋር በተያያዘ የላቀ አበርክቶ እንዳለው አብራርተዋል።
የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ መስፍን በበኩላቸው ለሚገነቡት የአጸደ ህጻናት እና ለአቅመ ደካሞች የቤት ግንባታ በአጠቃላይ በትንሹ 24 ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ወጪው የህጻናቱን የደብተር፣ የእስክሪፐቶ እና ሌሎች የትምህርት ቁሳቁሶችን የሚሻፍን መሆኑን ገልጸዋል ።
የአድማስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሞላ ጸጋዬ ተቋማት ፈቃድ እንዲያገኙ ማሟላት ከሚገባቸው መስፈርት አንዱ የማህበረስብ አገልግሎት በመሆኑ ተቋማቱ በተለያየ መንገድ የሚያደርጉትን የማህበሰብ አገልግሎት እንዲህ በተደራጀ መልኩ እንዲሆን ባለሥልጣኑ ከመንግስት የተረከበውን የአረንጓዴ አሻራ እና የክረምት በጎ ተግባራት ሀገራዊ ንቅናቄ ኃላፊት እንዲወጣ ለማስቻል በቦርዱ እና በተቋማቸው ስም ያላቸውን ዝግጁነት አረጋግጠዋል።
ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለአረንጓዴ አሻራ እና ለክረምት በጎ ተግባራት የያዙት በጀት ባይኖርም ለትምህርት የሚደረግ ድጋፍ የዜግነት ግዴታ በመሆኑ በራሳቸውና በቀድሞ ተማሪዎች እንዲሁም በሌሎችም ድጋፍ የሚጠበቅባቸው ኃላፊት ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ፡፡

Gallery

News Announcement
Share