Skip to content
Newsroom

ባለሥልጣኑ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በመገኘት የክረምት በጎ ተግባራት መረሀ ግብር አከናውነ

ETA Education & Training Authority September 16, 2026 1 min read
ባለሥልጣኑ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በመገኘት የክረምት በጎ ተግባራት መረሀ ግብር አከናውነ

ባለሥልጣኑ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በመገኘት የክረምት በጎ ተግባራት መረሀ ግብር አከናውነ

የኢፊዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር በቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ በመገኘት የክረምት በጎ ተግባራት መረሀ ግብር አከናውኗል።
የባለሥልጣኑ የእውቅና ስታንዳርዴዜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ድንኳና ንጉሳ ቀነኢ በመንግስት በተቀመጠ አቅጣጫ መሠረት የክረምት በጎ አድራጎት ሥራዎችን ለማከናወን በክልሉ መገኘታቸውን ገልጸው በዚህም ባለሥልጣኑ ለትውልድ ግንባታ መሠረት ከመጣል አንጻር ያለው ሚና የጎላ በመሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት መወሰኑን ገልጸዋል፡፡
በመረሀ ግብሩ ላይ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ተመስገን ዲሳሳ እና ምክትል የቢሮ ኃላፊው አቶ በሺር አብዱረሂም ፤ የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ (አደረጃጀት) ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኡሱማን አህመድ እና ሌሎች የሚመለከታቸው የክልሉ አመራሮች እንዲሁም የባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና በባለሥልጣኑ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና እና አጠቃላይ ትምህርት ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ስራ አስፈጻሚ ተገኝተዋል፡፡
ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትመህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ጎን ለጎን ለ500 ተማሪዎች የደብተር፣የቦርሳ፣ የእርሳስ እና የእስኪሪፕቶ ድጋፍ ተደርጓል። በመረሀ ግብሩ ባለሥልጣኑ የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት እና የችግኝ ተከላ ተደርጓል፡፡
ባለሥልጣኑ ባለፈው ዓመት በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመገኘት የአንድ አቅመ ደካማ ቤት ግንባታ እና የችግኝ ተከላ መረሀ ግብር ማከናወኑ ይታወሳል፡፡
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

Gallery

News Announcement
Share