Skip to content
Newsroom

ማስታወቂያ ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ!

ETA Education & Training Authority July 06, 2026 1 min read
ማስታወቂያ ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ!
ባለሥልጣኑ በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጮች አስተያየታችሁን መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
✔️ https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A ሊንኩን ወይም ማስፈንጠሪያውን በመጫን አስተያየት መስጫውን ማግኘት ትችላላችሁ፤ ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ ስትጨርሱ (submit) የሚለውን በመጫን አስተያየታችሁን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
✔ ማሻሻያ የተደረገበትን ረቂቅ አዋጅ በባለሥልጣኑ በዌብሳይት www.neta.gov.et የምታገኙ ይሆናል፡፡
✔ ለሚኖራችሁ ማንኛውም አስተያየት በባለሥልጣኑ ኢ-ሚይል አድራሻ Info@eta.et ላይ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
✔ በአካል ቀርባችሁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን መስጠት ለምትፈልጉ የፊት ለፊት (የገጽ ለገጽ) የመወያያ መድረክ ስለምናዘጋጅ በቀጣይ ቀኑን ፣ሰዓቱን እና ቦታውን የምናሳውቃችሁ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።
News Announcement
Share