Skip to content
Newsroom

በከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ 988/2016 መሠረት አጫጭር ስልጠና፤የተማሪ ቅበላ መጠን ጥያቄ፤ፕሮግራም ማስፋፊያ ጥያቄ፤ተጨማሪ ካምፓስ ጥያቄ እና ተጨማሪ ፕሮግራም ጥያቄ ማለት፡-

ETA Education & Training Authority August 18, 2026 1 min read
በከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ 988/2016 መሠረት አጫጭር ስልጠና፤የተማሪ ቅበላ መጠን ጥያቄ፤ፕሮግራም ማስፋፊያ ጥያቄ፤ተጨማሪ ካምፓስ ጥያቄ እና ተጨማሪ ፕሮግራም ጥያቄ ማለት፡-

በከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ 988/2016 መሠረት አጫጭር ስልጠና፤የተማሪ ቅበላ መጠን ጥያቄ፤ፕሮግራም ማስፋፊያ ጥያቄ፤ተጨማሪ ካምፓስ ጥያቄ እና ተጨማሪ ፕሮግራም ጥያቄ ማለት፡-

#አጫጭር_ስልጠና_ማለት_፡-
ማንኛውም ተቋም የከፍተኛ ትምህርትን ወይም የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ሊያግዝ የሚችል ተጨማሪ እውቀትንና ክህሎትን ለማስተላለፍ የሚሰጥ ማንኛውም ስልጠና ነው።
#የተማሪ_ቅበላ_መጠን_ጥያቄ_ማለት_፡-
ተቋማት ባላቸው የግብዓትና የሰው ሀይልመጠን ለማስተማር የሚፈቀድ የተማሪ ቁጥር ብዛት ጥያቄ ነው።
#ፕሮግራም_ማስፋፊያ_ጥያቄ_ማለት_፡-
ማንኛውም ተቋም ቀድሞ ፈቃድ ባገኘበት ፕሮግራም በተፈቀደለት የተማሪ ቁጥር ላይ ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል በመስፈርቱ መሠረት ተጨማሪ የግብዓት እና የሰው ሃይል ተሟልቶ የሚቀርብ ጥያቄ ነው።
#ተጨማሪ_ካምፓስ_ጥያቄ_ማለት_፡-
ማንኛውም ተቋም ቀደም ብሎ ፈቃድ ካገኘበት ካምፓስ ውጪ አዲስ ካምፓስ ለመክፈት የሚቀርብ ጥያቄ ነው።
#ተጨማሪ_ፕሮግራም_ጥያቄ_ማለት_፡-
ማንኛውም ተቋም ፈቃድ ካገኘበት ፕሮግራም ዉጪ ሌላ አዲስ ተጨማሪ ፕሮግራም ለመክፈት የሚቀርብ ጥያቄ ነው።
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

News Announcement
Share