በዓለም ዓቀፍ፣ የማህበረሰብ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት መመሪያ 992/2016 መሠረት በኢትዮጵያ የውጪ ሀገር የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ፈቃድ ጠያቂ ትምህርት ቤት የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች አሟልቶ ሲገኝ ባለሥልጣኑ ፈቃድ ይሰጣል
** አግባብ ካለው የመንግስት ተቋም አንዲሁም ከየሀገሮቻቸው ኤምባሲዎች በማህበረሰቡ ስም ስለሚቋቋመው ትምህርት ቤት የተሰጠ የእውቅና ማረጋገጫ፤
** ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር የተደረገ የስምምነት ሰነድ እና የትምህርት ቤቱን ደረጃ የሚመጥን ግብአቶችን ማሟላት፤
** የሰው ሃብት ቅጥር፣ እድገትና ስንብት፣ መረጃዎች እና አስፈላጊ ሰነዶች፤እና
** ለትምህርት ቤትነት የሚመጥን አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ አደረጃጀትን የሚያሳይ ሰነድ እና የትምህርት ቤቱ መተዳደሪያ ደንብ፣ የመመስረቻ ሰነድ እና የራሳቸው የትምህርት ካላንደር ሲያቀርብ ፍቃድ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።