በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተቋም እና የፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ መመሪያ 991/2016 መሠረት ስለተቋም እና የፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ ቅድመ ሁኔታዎች

በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተቋም እና የፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ መመሪያ 991/2016 መሠረት ስለተቋም እና የፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ ቅድመ ሁኔታዎች ----------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------- #የተቋም_እውቅና_ቅድመ_ሁኔታ ማንኛውም ተቋም የተቋም እውቅና ሊጠይቅ የሚችለው የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላት ሲችል ብቻ ነው:: ** ተቋሙ ከባለስልጣኑ በከፍተኛ የትምህርት የማስተማር ፈቃድ ያለው ወይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እንዲሰራ በፌደራል ወይም በክልል መንግስታት ስልጣን ባለው አካል የተቋቋመ ሊሆን ይገባል፤ ** ተቋሙ ቢያንስ በአንድ ፕሮግራም አንድ ዙር ያስመረቀ መሆን ይገባዋል፤ ** ተቋሙ የተቋም እውቅና ከመጠየቁ በፊት በባለስልጣኑ ተቋማዊ ጥራት ኦዲት ያካሄደ መሆን አለበት፤ እና ** ተቋሙ በባለስልጣኑ ለተቋም እውቅና አሰጣጥ ሥራ የተቀመጠውን የክፍያ መጠን መክፈል ይኖርበታል፡፡ #የፕሮግራም_እውቅና_ቅድ_መሁኔታ ማንኛውም ተቋም የፕሮግራም እውቅና ሊጠይቅ የሚችለው የሚከተሉትን ማሟላት ሲችል ብቻ ነው:: ** ተቋሙ ከባለስልጣኑ በፕሮግራሙ የማስተማር ፈቃድ ሊኖረው ይገባል፤ ** ተቋሙ የፕሮግራም እውቅና ጥያቄ ማቅረብ የሚችለው ፈቃድ ባገኘበት አግባብና ደረጃ መሆን ይገባዋል፤ ** ተቋሙ በፕሮግራሙ ቢያንስ አንድ ዙር ተማሪዎችን ያስመረቀ መሆን ይገባዋል፤ እና ** ተቋሙ በባለስልጣኑ ለፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ ሥራ የተቀመጠውን የክፍያ መጠን መክፈል ይኖርበታል፡፡ የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።