በከፍተኛ እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት የክትትልና ቁጥጥር መመሪያ 987/2016 መሠረት በባለሥልጣኑ ከተፈቀደው የተማሪ ቁጥር በላይ መዝግቦ ሲያስተምር ስለተገኘ ተቋም፡-

በከፍተኛ እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት የክትትልና ቁጥጥር መመሪያ 987/2016 መሠረት በባለሥልጣኑ ከተፈቀደው የተማሪ ቁጥር በላይ መዝግቦ ሲያስተምር ስለተገኘ ተቋም፡- --------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------- ** ማንኛውም ተቋም በባለሥልጣኑ ከተፈቀደው የተማሪ ቁጥር በላይ መዝግቦ ማስተማር አይችልም፤ ** ተቋማት ከተፈቀደላቸው የተማሪ ቁጥር በላይ ቅበላ ማድረግ ሲፈለጉ ለባለሥልጣኑ ጥያቄ በማቅረብ ፈቃድ ማግኘት ይኖርባቸዋል ፤ ** ከላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ በመተላለፍ አንድ ተቋም ከተፈቀደለት የተማሪ ቁጥር እስከ 20% ጭማሪ አድርጎ ሲገኝ በትምህርት መስኩ ለ1 ዓመት አዲስ ተማሪ እንዳይቀበል ቅጣት ይጣልበታል፤ ** ከተፈቀደለት የተማሪ ቁጥር ከ 20% በላይ ጭማሪ ተቀብሎ የተገኘ ከሆኑ በትምህርት መስኩ ለተከታታይ ለ2 ዓመታት አዲስ ተማሪ እንዳይቀበል ቅጣት ይጣልበታል፤ እና ** ከላይ የተጠቀሰውን የተላለፈ ተቋም የትምህርት መስክ እንዲዘጋ ይደረጋል። የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።